ሕዳር 26/2018 (አሐዱ ሬዲዮ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከማርበርግ ቫይረስ ምልክቶች ታይተውባት፤ በለይቶ ማቆያ የሕክምና ክትትል ሲደረግላት የቆየች ታካሚ ከማርበርግ ቫይረስ በሽታ ነፃ መሆኗ ተገልጿል፡፡
የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ አራተኛዋ ሰው ከማርበርግ ቫይረስ በሽታ ታክማ ነፃ ሆና ወደ ቤተሰቦቿ መቀላቀሏን ገልጸዋል።

ታካሚዋ የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምልክቶችን አይታ በፍጥነት ወደ ሕክምና ተቋም መምጣቷ ለመዳኗ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለው ጠቁመው፤ የሕክምና ማዕከሉ ጤና ባለሙያዎች ያደረጉትን ትጋትና ርብርብ ማመስገናቸውን ጤና ሚኒስቴር ለአሐዱ በላከው መግለጫ አስታውቋል።
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ