ጥቅምት 10/2018 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ አስክሬን ፒያሳ በሚገኘው ኑር መስጂድ የዱዓ እና የሽኝት ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል።

Post image

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ አስከሬን ለ40 ዓመታት ባስተማሩበት ኑር መስጂድ ሶላተል ጀናዛ ተሰግዶበታል።

በሽኝት መርሐ ግብሩ ላይም ኡለማዎች፣ ደረሳዎች፣ ኡስታዞች እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል፡፡

Post image

በአሁኑ ወቅት አስክሬናቸው ወደ ሚሊኒየም አዳራሽ እየተሸኘ ሲሆን፤ ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የክብር ሽኝት ከተረገላቸው በኋላ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ሥርዓተ ቀብራቸው የሚፈፀም ይሆናል።

ፎቶ፦ ኢዜአ እና ኢቢሲ
‎#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ