ሰኔ 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) እንደ አውሮፓ አቆጣጠ 2022 የዓለም ጤና ድርጅት ባጠናው ጥናት በዓለም አቀፍ ደረጃ በሱስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር ከ292 ሚሊዮን መብለጡ ተገልጿል።
የጤና ሚኒስቴር የዓለም ፀረ-ሱስ ቀንን ምክንያት በማድረግ "የቅድመ መከላከል፤ የማከም እና የተሃድሶ አገልግሎት ለሁሉም" በሚል መሪ ቃል፤ ለሚዲያ ባለሙያዎችና ለጤና ባለሞያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና በቢሾፍቱ ከተማ ተሰጥቷል።
በዚህም በተሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዓለም አቀፍ ደረጃ 65 ነጥብ 5 የሚሆኑት የሱስ ተጠቂ የሆኑት ወንዶች መሆናቸው ተገልጿል።
የጤና ሚኒስትር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የህብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሻሻል ሱሰኝነትን ጨምሮ በተለይም ተላላፊ፣ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን እና የአእምሮ ጤና ችግር ለመከላከልና ለመቆጣጠር ትኩረት በመስጠት እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በዚህም የዓለም የፀረ-ሱስ ቀንን ምክንያት በማድረግ በኢትዮጵያ ከሰኔ 18 እስከ ዛሬ ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም በተለያዩ ቦታዎች የተከበረ ሲሆን፤ እንደ ሀገር እየጨመረ የመጣው ሱሰኝነት አሳሳቢ እየሆነ ነው ተብሏል።
በተለይ አምራች ሀይል የሚባለው ወጣቱ የማህበረሰብ ክፍል በሱስ ተጠቂቱ ከፍተኛ ቁጥር ይይዛል ተብሏል።
በተጨማሪም ሚኒስቴር መስራያ ቤቱ የአዕምሮ ጤና ሕክምናን በሁሉም የግልና የመንግሥት ተቋማት ለማስፋት ብሎም ግንዛቤ ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል።
ይህም እንደሀገር በጤናው ዘርፍ፣ በኢኮኖሚው እና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ ነው ተብሏል።
ሱስ ታክሞ የሚድን የጤና ቀውስ በመሆኑ በሱስ የተጠቁ ግለሰቦችን ከሱስ እንዲወጡ ማድረግ መንከባከብ የሁሉም ሰው ሀላፊነት ሊሆን እንደሚገባ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናውን የሰጡ የዘርፉ ባለሞያዎች አሳስበዋል።
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ
በዓለም አቀፍ ደረጃ በሱስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር ከ292 ሚሊዮን መብለጡ ተገለጸ
