የራስ ደስታ ዳምጠው የወርቅ ሜዳሊያ ለጨረታ መቅረቡን ተከትሎ ቤተሰቦቻቸው ሜዳልያው እንዲመለስ ጠየቁ

ሕዳር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በጣልያን ዳግም ወረራ ወቅት የተገደሉት የራስ ደስታ ዳምጠው የኮከብ ቅርጽ ያለው የወርቅ ሜዳሊያ ለጨረታ መቅረቡን ተከትሎ፤ ቅርሱን ለማስመለስ እንደሚፈልጉ ቤተሰቦቻቸው ገልጸዋል።