ሸቀጦች ላይ እየተደረገ ያለዉ የዋጋ ጭማሪ ፈጣን በመሆኑና የኢትዮጵያ ብር የመግዛት አቅሙ መዳከም ጋር መጣጣም ባለመቻሉ፤ የዋጋ ንረቱ እንደሚከሰት በጥናቱ ተገልጿል።
በተጨማሪም የዋጋ ንረቱ የማህበረሰቡን የአኗኗር ዘይቤ እንደሚቀይረዉና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸዉ ማህበረሰቦች ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ስለማሳደሩም ተመላክቷል።
እንዲሁም የውጭ ምንዛሬ እጥረቱና ኢኮኖሚው የተመጣጠነ አለመሆኑን የተቆመው ማህበሩ፤ የገበያ መር ስርዓት ሊያረጋጋው እንደማይችልም ገልጿል።
ሌላዉ በጥናቱ እንደታየዉ ከሆነ ለኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ መሻሻል ማነቆ ከሆኑት ውስጥ፤ የሰላም መደፍረስ፣ በቂ ጥሬ እቃ አለመኖር፣ ደካማ የሆነ መሰረተ ልማትና ቢሮክራሲ መብዛት ዋነኞቹ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
እንደ መፍትሔ ሀሳብ መንግሥት በረጅም ጊዜ የልማት ዕቅዶቹ ላይ የሚያወጣውን ወጪ በመቀነስ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ዜጎች የማኅበራዊ ድጋፍ ማድረግ እንዳለበት ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት በሚቀጥሉት ወራት ወደ 26 ነጥብ 1 ከፍ ሊል እንደሚችል ተመላከተ
ሕዳር 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ ያለዉ የዋጋ ንረት በሚቀጥሉት ወራት ከነበረዉ 16 ነጥብ 1 በመቶ በ10 በመቶ ጨምሮ፤ 26 ነጥብ 1 በመቶ ሊደርስ እንደሚችል የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህበር ያወጣው የፖሊሲ ጥናት አመላክቷል።