ጥር 2/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ኢትዮጵያ በአሜሪካ ካሊፎርኒያ ግዛት ሎስ አንጀለስ የተከሰተው ሰደድ እሳት በሰው ሕይዎት እና በንብረት ላይ ባደረሰው ጉዳት የተሰማትን ጥልቅ ሐዘን ገልጻለች፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፤ በደረሰው ጉዳት ኢትዮጵያ ማዘኗን አስታውቋል፡፡

በዚህ አስቸጋሪ ወቅት የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ከአሜሪካ መንግሥትና እንዲሁም በሎስ አንጀለስ አካባቢ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጎን መሆናቸውን አረጋግጧል፡፡