ሕዳር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአዲስ አበባ ከተማ ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የሚገኝ አንድ በርበሬ ከባዕድ ነገር ጋር ተቀላቅሎ የሚመረትበት መጋዘን ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገልጿል።
ሕዳር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ በየዓመቱ 5 ሺሕ ሴቶች በማህፀን በር ካንሰር በሽታ የሚያዙ ሲሆን፤ 3 ሺሕ የሚሆኑት ደግሞ ሕወታቸው እንደሚያልፍ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ የዘርፉ አስተባባሪ አቶ ወንድወሰን በርሄ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡
ሕዳር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኦሮሚያ ክልል መንግሥት እና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አመራሮች የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ፤ የሠራዊቱ አባላት ወደ ተዘጋጀላቸው ካምፕ መግባት መጀመራቸው ተገልጿል፡፡
ሕዳር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በጣልያን ዳግም ወረራ ወቅት የተገደሉት የራስ ደስታ ዳምጠው የኮከብ ቅርጽ ያለው የወርቅ ሜዳሊያ ለጨረታ መቅረቡን ተከትሎ፤ ቅርሱን ለማስመለስ እንደሚፈልጉ ቤተሰቦቻቸው ገልጸዋል።
ሕዳር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኦሮሚያ ክልል ዱከም ከተማ በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ሁለት ሙሉ የነዳጅ ቦቴ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የኦሮሚያ ንግድ ቢሮ አስታውቋል።
ሕዳር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙና የፕላስቲክ ምርቶችን በመጠቀም ምርት የሚያሽጉ፣ መሸጫ መለወጫ የሚደደርጉ ኢንዱስትሪዎች፤ ማስጠንቀቂያ እንደደረሳቸው የከተማ አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ለአሐዱ ተናግሯል።
ሕዳር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ ከ17 ነጥብ 6 በመቶ በላይ ሰዎች የአካል ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው የአለም ጤና ድርጅትና አለም ባንክ ያጠናው ጥናት መጠቆሙ ተገልጿል፡፡
ሕዳር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የብልፅግና ፓርቲ አመስተኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ የፓርቲውን ጉዞ አስመልክቶ በተገለጸው ልክ፤ ያለፋት አምስት ዓመታት የስኬት ዓመታት አልነበሩም ሲሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀሳባቸውን ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡
ሕዳር 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ እንደቴሌግራም፣ ኢንስታግራምና ፌስቡክ በመሳሰሉት የበይነ መረብ አውታሮች በመጠቀም የሚሸጡ የሚለውጡ ነጋዴዎች እየተበራከቱ መምጣታቸውን ተከትሎ፤ ከግብይቶች መንግሥት ማግኘት ያለበትን ታክስ እያሳጡት መሆኑን የፓሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አስታውቋል።
ሕዳር 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለምክር ቤቱ ዕዉቅና ከመስጠት ዉጪ አማራጭ የለዉም ሲል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፖርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ገልጿል፡፡
ኤፍ ኤም 94.3